˝በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው 7ኛው ዙር ሀገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር በምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ ዶቦ ጡጦና በሬሳ ቀበሌ ላይ በማለዳው ተጀምሯል!!
˝በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው 7ኛው ዙር ሀገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር በምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ ዶቦ ጡጦና በሬሳ ቀበሌ ላይ በማለዳው ተጀምሯል!! ( ሐምሌ 24/2017 ቡታጅራ) ˝በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል እንደ ሀገር 700 ሚሊዮን ችግኞች በመትከል የዘንድሮ ሀገራዊ 7ኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው። አንደ ምስራቅ ጉራጌ ዞን ሀገራዊ ተልዕኮ ለመወጣት ከችግኝ ዝግጅትና አቅርቦት ጀምሮ በርካታ ተግባራት የተከናወኑበት ይህ የአረንጓዴ ዐሻራ የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር ጀንበር ወጥታ እስከምትጠልቅ ባለዉ ጊዜ በከፍተኛ ትጋት ቀኑን ሙሉ የሚካሄድ መሆኑንም ተገልጾዋል። በዚህም መላው የዞኑ ማህበረሰብ በነቂስ ማልዶ ወጥቶ በአረንጓዴ ዐሻራዉ መስክ ታላቅ የታሪክ ዐሻራ እያኖረ የሚገኝ ሲሆን፤ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ፣ የጥላና የአፈር መሸርሸርን የሚከላከሉ ችግኞች እየተተከሉ ነው። በአጠቃላይ መርሃ – ግብሩ በመትከል ማንሰራራት በሚል እየተካሄደ ሲሆን፤ እንደ ሀገር 700 ሚሊዮን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተተከሉበት የሚገኝበትም ነው።